Tuesday, December 3, 2013

የጋምቤላዉ ተፈናቃይ በብሪታኒያ መንግስት ላይ የመሰረተው ክስ መታየት ጀመረ


ከሳሽ እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በሠፈራ መርሐ-ግብሩ በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማፈናቀል፥ ማሰደዱን የብሪታንያ መንግሥት እያወቀ ለኢትዮጵያ መንግሥት በተለይም ለፀጥታ አስከባሪዎች ማሰልጠኛ ርዳታ መስጠቱ ለተፈፀመዉ በደል አባሪ ተባባሪ መሆኑን አመልካች ነዉ። የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ከቤት ንብረቴ አፈናቀሉኝ፥ አሠሩኝ፥ ደበደቡኝም ያሉ አንድ የጋምቤላ መስተዳድር ነዋሪ የኢትዮጵያን መንግሥት ይደግፋል ያሉትን የብሪታንያ መንግሥትን ከሰሱ። ሥማቸዉ ለደሕንነታቸዉ ሲባል በሚስጥር የተያዘዉ ኢትዮጵያዊ በጠበቆቻቸዉ በኩል የመሠረተቱትን ክስ የብሪታንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትናንት ማድመጥ ጀምሯል። ከሳሽ እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በሠፈራ መርሐ-ግብሩ በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማፈናቀል፥ ማሰደዱን የብሪታንያ መንግሥት እያወቀ ለኢትዮጵያ መንግሥት በተለይም ለፀጥታ አስከባሪዎች ማሰልጠኛ ርዳታ መስጠቱ ለተፈፀመዉ በደል አባሪ ተባባሪ መሆኑን አመልካች ነዉ። የዶይቼ ቬይሌ ወኪድልነሳ ጌታነሕ ለንደ   አጭር ዘገባ ለማዳመጥ እዚህ ጋር ይጫኑ::

No comments:

Post a Comment