በስደት ላይ ሞት እንዴት ያሳዝናል። አገሩም ላይ ሳይደላው፡ በስደት ላይ እንደወጣ ለቀረው የሙያ አጋራችን ነፍስህ በሰላም ትረፍ። የህውሃትን ወከባ እና አፈና አመለጥኩ ሲል በዚህ መልኩ መሞት ግን ህይወት አንዳንዴ ለምን በጣም ብዙ ጊዜ በየዋሃን ላይ እንደምትጨክን ያሳያል። የሚሊዮን ሞት ለቤተሰቡ እና ለሙያ አጋሮቹ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ከራሴ ልምድ አውቀዋለሁ። ወይ ነዶ ስደት ለወሬ አይመችም። ለሚሊዮን ቤተሰቦች፡ወዳጆች እና የሙያ ባልደረቦች መጽናናቱን ይሰጣችሁ ዘንድ ምኞቴን እየገለጽኩ ይህ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ወይ ልብ ይስጠው ወይ ደግሞ መጨረሻውን ያቅርበው፡ አሜን።
ከሞቱ
አሟሟቱ ካገሩ በወጣ በወር ከአስር ቀኑ በሞት
ያጣነው ጋዜጠኛ ሚሊየን ሹርቤ የመጨረሳዎቹ
ቀናትጋዜጠኛ ሚሊዮን በመጨረሻዎቹ ሰዓታት….
የሚሊዮን አሟሟት እንዳስረዳችሁ ለጠየቃችሁኝ …
ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ በኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ከ12 አመት በላይ የሰራ ወጣት ጋዜጠኛ “ነበር”፡፡ በነሃሴ ወር ውስጥ በመንግስት ወከባ ህይወቱን ከእስር ለማትረፍ ተሰዶ ወደሀገሩ በሳጥን ለመመለስ እየጠበቀ ያለ ወጣት ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ…ሚሊዮን፡፡ ተስፋ የነበረው ስደተኛ ጋዜጠኛ የመልካም ባህሪ እና ስብእና ባለቤት የነበረው ሚሊዮን፣ ስለሀገሩ ፍቅር ብዙ መሰናክሎችን ሊጋፈጥ ስደትን መርጦ ባሰበበት ሳይሆን በታሰበለት ሊኖር የተገደደው ሚሊ እንደወጣ በሰው ሀገር ልጄን እህቶቼን ቤተሰቦቼን ሃገሬን እንዳለ በድንገት