Showing posts with label Birhanu Nega. Show all posts
Showing posts with label Birhanu Nega. Show all posts

Wednesday, July 9, 2014

የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ የነበሩት እና በየመን መንግስት ባለስልጣናት ተላልፈው የተሰጡት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በኢቴቪ ላይ ቀረቡ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ ለማምራት ባለፈው ሳምንት ሰንዓ ዓየር ማረፊያ ላይ አውሮፕላን ለመቀየር ሲሉ በየመናውያን የጽጥታ ሃይሎች ከተያዙ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ የተላለፉ የሚታወስ ሲሆን፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ እይታ የቀረቡት መንግስት በሚቆጣጠረው የቴሌቪዥን ጣቢያ ነው። ዜና አቅራቢው ተመስገን በየነ ከወትሮው ለየት ባለ ንቃት እና ፈገግታ በመታጀብ አያቱ ሊሆኑ የሚችሉትን ግለሰብ አንተ እያለ በመዘርጠጥ ዜናው ሲያስደምጥ ነበር። አቶ አንዳርጋቸው በዚሁ ተቀናብሮ (ደበበ እሸቱ፡ ብርቱካን ሚዴቅሳ፡ ስዊድናውያን ጋዜጠኞቹን እና ሌሎችም በመቶ የሚቆጠሩ የቀድሞ እስረኞች ልብ ይሏል) በተሰጣቸው የንስሃ በሚመስል ቃለ ምልልስ ላይ፡ በእስር ላይ መዋላቸውን በጸጋነት እንደሚቀበሉት ሲናገሩ ተደምጠዋል። አጃኢብ ነው፡ ውድ የኢትዮጵያ ልጅ ስማ፣ ላልሰማ አሰማ ኢትዮጵያ ውስጥ ማእከላዊ የሚባል እስርቤት ሰላምህን የሚሰጥ ስለሆነ፡ ቦታ እንዳያመልጥህ ተሽቀዳደም። እቺ የተቀነባበረች ዜና የቀረበችው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የአቶ አንዳርጋቸው ደህንነት እንዳሳሰባቸው በመግለጽ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ዓለምዓቀፍ ዘመቻ በጀመሩበት ሰዓት መሆኑ እነሱም ድራማ መስራት አይሰለቻቸው እኛም መመልከት ያሰኛል። የብሄራዊ ደህንነት ድርጅቱ በተጨማሪ ለተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች እና ደጋፊዎች፡ ለጋዜጠኞች እና ጦማሪያን እንዲሁም በዞን ዘጠኝ ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ በሙሉ በጸረሽብሩ "ህጋችን" ለእስር ከመዳረግ እንደማንድን በገደምዳሜ ተነግሮናል። ለማንኛውም ተመስገንን እንዲህ ያስፈነደቀው ዜና ከዚህ በታች በሚገኘው ቪድዮ ላይ መመልከት ይችላሉ። 

Friday, October 4, 2013

No Ties with Egypt: Ginbot-7

Andargachew Tsigie, Secretary of Ethiopia's opposition Ginbot 7 movement , disclosed this on Sunday September 29, 2013 at a public gathering held here in Stockholm with members and supporters of the organization who reside in Sweden. Some participants of the gathering posed this sensitive question to know about Ginbot-7's positions regarding the controversial Abay mega hydro-power plant which recently strains relations between

ግንቦት ሰባት ከግብጽ መንግስት ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው አስታወቀ።


ይህንን ያስታወቁት የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እሁድ መስከረም አስራዘጠኝ ሁለትሺህ ስድስት በስዊድን ዋና ከተማ የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል ከአባላቶቹ እና ደጋፊዎቹ ጋር ባካሄደው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ድርጅታቸው በኢትዮጵያ ያለው የህውሃት መንግስት እገነባለሁ ስለሚለው የአባይ ወንዝ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ የተነሳ የግብጽ መንግስት ኢትዮጵያውያን ተቃዋሚዎች ድርጅቶችን ያስታጥቃል እናንተስ