«....ማንም
ሰው ለመማርና ለመሠልጠን መድከም አለበት።» ዳግማዊ አጤ ምንሊክ ንጉሰነገስት ዘኢትዮጵያ
በ፲፰፻፺፰
ዓ.ም
ስለትምሕርት ያስነገሩት አዋጅ
«እናንተ አንድ ልብ ከሆናችሁ በምቀኝነት እርስ በርሳችሁ ተዋግታችሁ ካላለቃችሁ በቀር ኢትዮጵያን አገራችንን ለሌላ ለባእድ አትሰጧትም፤ ክፉም ነገር አገራችንን አያገኛትም። ነፋስ እንዳይገባባችሁ አገራችሁን በያላችሁበት በርትታችሁ ጠብቁ፤ ወንድሜ ወንድሜ እየተባባላችሁ ተደጋገፉ፤ የኢትዮጵያን ጠላት ተጋግዛችሁ ተደንበር መልሱ። የኢትዮጵያ ጠላት ባንዱ ወገን ትቶ ባንድ ወገን ቢሄድና ደንበር ቢገፋ፤ በኔ ወገን ታልመጣ ምን ቸገረኝ ብላችሁ ዝም አትበሉ፤ ያ ጠላት በመጣበት በኩል ኁላችሁም ሄዳችሁ አንድነት ተጋግዛችሁ ጠላታችሁን መልሱ እስከ እየቤታችሁ እስኪመጣ ዝም ብላችሁ አትቆዩ» ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ፤ ግንቦት ፲ ቀን ፲፱፻፩ ዓ.ም
ልክ በዛሬዋ እለት ከመቶ ዓመት በፊት እኝህ የኢትዮጵያንም ሆነ የመላው ጥቁር ዘር ታሪክ የቀየሩት እና ከዘመናቸው ቀድመው የተወለዱት ኢትዮጵያዊ መሪ ለዓመታት ሲታገሉት የነበረው ህመማቸው አሸንፏቸው እችን ዓለም ተሰናበቱ። ኢትዮጵያዊ ታሪክ ጸሃፊ መርስዔ
ኀዘን ወልደ ቂርቆስ -
ትዝታዬ
- ስለራሴ
የማስታውሰው ፲፰፺፩ - ፲፱፳፫ በሚለው መጽሃፋቸው ዳግማዊ አጤ ምኒልክ በህልፈት ሲለዩ የነበረውን ሁኔታ በዚህ መልኩ ነበር የገለጹት፦
