Thursday, April 26, 2012

የኢትዮጵያውያን የተቋውሞ ሰልፍ በስቶክሆልም ፳፻፬ ዓ/ም

በስዊድን አገር የሚኖሩ ቁጥራቸው ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ሚያዚያ ፩፯/፳፻፬ ዓ/ም ከቀኑ ከሰባት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት በኢትዮጵያ ቆንስል ፊት፡ለፊት በመገኘት የኢህአዴግ መንግስት እያካሄደ ያለውን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ ዜጎችን ከሚኖሩበት ቀዬ የማፈናቀል ዘመቻ፡ በሃይማኖቶች ጣልቃ ገብነት፡ በስመ ልማት የመሬት ቅርጫ፡ እንዲሁም ሴቶችንና ህጻናትን ለዘመናዊ ባርነት የመዳረግ ወንጀሎችን እንዲያቆም ተቋውሟቸውን አሰሙ። ከዚህም በተጨማሪም በቃሊቲና በሌሎች እስርቤቶች በመማቀቅ ላይ የሚገኙ የህሊና እስረኞች ባስቸኳይ እንዲፈቱ፡ የህግ የበላይነት እንዲከበር፡ የዜጎች የመናገር፡የመጻፍ፡የመሰብሰብና በነጻ የማሰብ መብቶች እንዲከበሩ የስራ ማቆም አድማ ላይ በተሳተፉ መምህራን ላይ የሚካሄደውን መዋከብ የመለስ ዜናዊ መንግስት ባስቸኳይ እንዲያቆምና ስልጣኑን በህዝብ ለተመረጠ መንግስት እንዲያስረክብ አሳስበዋል። ተሰላፊዎቹ የኢትዮጵያን ሰንደቅ በማውለብለብ እና ልዩ ልዩ ቀስቃሽና ወቅታዊ መፈክሮችንና መዝሙሮችን ካሰሙ በኋላ በመጨረሻም የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች እነዚህ በዓለምዓቀፍ ህግ የተደነገጉ ሰብዓዊና የዜግነት መብቶች በኢትዮጵያ እንዲከበሩ የሚያሳስቡ ጥያቄዎቻቸውን በደብዳቤ መልክ ለቆንስላው ተወካይ በማቅረብ የተቋውሞ ሰልፉ ተጠናቋል።

Sunday, April 22, 2012

ከፈላ ያስከፍላል ፍዳ

ከኢትዮጵያ ወጥታ አረብ አገር የገባች ነፍስ
ፍዳ ትበላለች ተጠፍራ እንዳጋሰስ
ይቅርታ ለተወለጋገደችው ስንኝ  ተብዬ። ችግር በቂቤ ያስበላል ትል ነበር እማዬ ነፍሷ በሰላም ይረፍና ቂቤ እንዲህ አልማዝ መሆኑን ሳታይ በግዜ ተገላገለች እንጃ አሁን ተረቱ ተለውጦ ከሆነ እንዴ መቼም እነንትና ካልሆኑማ ማንም በቂቤ የሚተርትም/የሚቀልድም ያለ  አይመስለኝም። 
ወደ ተነሳሁበት ጉዳይ ልመለስ፦መቼም አብዛኛዎቻችሁ ይሄንን ከዚህ በታች የሚገኘውን በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵውያውያን እህቶቻችን/ልጆቻችን የሚደረገውንና እንኳን በሰው ልጆች ላይ በእንስሳት ላይ መፈጸም የሌለበትን ጨካኝ፡ኢሰብዓዊ እና ዘግናኝ ድርጊት የሚያሳይ ፊልም ሳታዩ አትቀሩም ወይም የወሬ ወሬ የሰማችሁ ይመስለኛል። ይሄ ፊልም የሚያሳያው በአንድ የሳውዲ አረቢያ ከተማ ውስጥ በኢትዮጵውያን ሴቶች ወገኖቻችን ላይ ስለሚፈጸመው ግፍ ሲሆን፦ልብ ማለት ያለብን ግን እንዲህ ዓይነቶቹ ኢሰብዓዊ ድርጊቶች በመላው አረብ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ሆኑ ከሶስተኛው ዓለም በመጡ ረዳትም ሆነ ደጋፊ የሌላቸው የጉልበት/የቤት ሰራተኞች ላይ የሚፈጸም የእለት ተእለት ተራ ድርጊት እየሆነ ከመጣ ዓመታት ተቆጥረዋል። ለዚህም እንደዋና ምክንያት የሚጠቀሰው ከፈላ የተባለውና በሳውዲ መንግስት ተዘጋጅቶ በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኙ አገራት በስፋት እየተሰራበት ያለው

Tuesday, April 17, 2012

Syrians in Sweden demand foreign intervention.

Early this evening (April 17, 2012) Syrians who reside in Sweden demonstrated in Stockholm to demand for more stronger pressure from international community against Syrian government to stop its killings and imprisonments of innocent Syrian protesters in Syria. Some of the speakers blamed China and Russia which vetoed against the UN's security council sanctions which could have stopped mass killings by Al-Assad's military & security apparatus.

Friday, April 13, 2012

Is the West Obsessed with awarding Ethiopian "Terrorist"?

Sorry, I don't want to confuse you so I just want to clarify this: when I say "terrorist", I meant to say these bunch of Ethiopian "terrorist" journalists who tried/are trying to "overthrow" Ethiopia's constitution using various lethal weapons like pens, papers as well as PCs- a very dangerous state of the art artillery. Eskinder Nega, is among one of them who used to incite violence by concluding his postings like this "fight Tyranny behind your PC". Even though, he was advised to stop his terrorist activities several times; he nevertheless continued his malicious and atrocious cyber crimes with the help of a PC. Our developmental and democratic government run out of its patience last September and jailed this "terrorist" (thanks to our efficient and the best ever intelligence service in the world) and if convicted will face death sentence: can you imagine how many millions of Ethiopians including me would sleep peacefully? After over 114 "terrorists" including two Swedish journalists have been arrested since last year in March; Ethiopia becomes one of the safest place in the world to live. But wait a minute, against this background; I read a very disturbing and upsetting story this morning