Saturday, January 4, 2014

ህውሃት ባለስልጣኖቹ ለኢሳት ቃለመጠይቅ እንዳይሰጡ አዘዘ

Ethiopian Satellite Television (ESAT)ኢሳት  ይህንን ዜና የዘገበው ታህሳስ ፳፭( ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ሲሆን ህውሃት ባለስልጣናቱ ማንኛውንም ቃለምልልስ ለኢሳት ቢሰጡ በአሸባሪነት  እንደሚከሰሱ አስታውቋል። የባለስልጣኖች አንደኛው መገምገሚያም ለኢሳት መረጃ በመስጠት እንደሚወሰን ከኢህአዴግ የመረጃ ክፍል የደረሰን መረጃ ያመለክቷል። መመሪያው ለህዝብ ግንኙነት ሰራተኞች፣ ለደህንነት ሰራተኞች፣ ለመንግስት ባለስልጣናት እና ለ ኮሚኒኬሽን ባለሙያዎች መተላለፉ ታውቋል።
የመንግስት ባለስልጣናት ለኢሳት መረጃ በመስጠት ድርጅቱን ህጋዊነት እያላበሱትና ሌሎችም ዜጎች አንዲናገሩበት እያደፋፈሩ ነው የሚል ምክንያት መሰጠቱ ታውቋል። ባለስልጣናቱ ከኢሳት በተጨማሪ ለአሜሪካ ድምጽ እና ለአንዳንድ ስማቸው ያልተጠቀሰ ድረገጾችም መረጃ እንዳይሰጡ ታዘዋል። መመሪያውን ያወጡት የብሄራዊ የመረጃ ደህንነት እና ኮሚኬሽን መስሪያ ቤት በጋራ በመሆን ነው። በዚህ ዙሪያ ተጨማሪ ዘገባ በሚቀጥሉት ቀናት ይዞ እንደሚቀርብ ኢሳት  ገልጿል።


No comments:

Post a Comment