Sunday, June 2, 2013

የ35ኛው ስቶክሆልም ማራቶን ኢትዮጵያውያን እድል ቀናቸው 35th ASICS Stockholm annual Marathon


በየዓመቱ እዚህ ስዊድን ዋና ከተማ በሚካሄደው የ35ኛው ስቶክሆልም ማራቶን ኢትዮጵያውያን እድል ቀናቸው። ሹምዬ ገርባ ኤቲቻ 2.16.13 ሰዓት በማስዝገብ 1ኛ ሲሆን እሱን ተከትሎ የገባው ደግሞ ኬኒያዊው ስቲቨን ቺሊሞ ሲሆን ኢትዮጵያዊው እንዳለ ተክለዓብ 2.18.29 ሰዓት በማስመዝገብ 3ኛ ሆኖ ውድድሩን አጠናቋል። ሹምዬ ይሄን በስቶክሆልም የተካሄደውን ውድድር ለሁለተኛ ጊዜ እንዳሸነፈ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ውድድሩን ካጠናቀቀ በኋላ በስዊድን ለሚገኘው ቲቪ4 ለሚባለው የቴሌቪዥን ማሰራጫ በሰጠው ቃለመጠይቅ ትናንትናው ውጤቱ እንዳልተደሰተና በሚቀጥለው ተመሳሳይ ውድድር የተሻለ ሰዓት ለማስመዝገብ እንደሚጥር ተናግሯል።
በሴቶች ምድብ የስዊድሽ ዜግነት ያላት ኢዛቤላ አንደኛ ስትሆን እሷን ተከትላ 2.41.57 ሰዓት በማስመዝገብ 2ኛ በመሆን ውድድሩን ያጠናቀቀችው ኢትዮጵያዊቷ ሃሊማ ሃሰን በሪሶ ስትሆን በሶስተኝነት የገባችው ደግሞ ስዊድናዊዋ ሯጭ ፍሪዳ ሉንደን ነበረች። ኢዛቤላ ይህንን ውድድር ለአምስት ተከታታይ ጊዜ ማለትም ከ 2008 እስከ 2011 እንደ አውሮፖውያኑ አቆጣጠር በማሸነፍ ብቸኛዋ የማራቶን ሯጭ ናት።
Ethiopia's Shumi Gerbaba Eticha and Sweden's Isabellah Andersson won men's and the women's titles of the 35tt ASCIS Stockholm annual Marathon on Saturday.
Ethiopian men marathoners came 1st and 3rd at 35th ASICS Stockholm annual Marathon. Shumie Gerba Eticha claimed the first place in the men's race with a time of 2:16:13 followed by Kenyan Stephen Chilmo with 2.17.51 and Endale Tekiab finished 3rd finishing with 2.18.29. It was Gerbaba's second victory since 2011. But however, he was not excited with his performance, telling reporters that he had hoped for a better result. Gerbaba told with interpreters local Swedish Channel TV4, "I hope to come back and improve the time."

In the women catageory, the Swedish marathoner Isabella Andersson came first with 2.33.49, Halima Hassen Beriso stood 2nd with 2.41.57 followed by Frida Lunden from Sweden crossing the finishing line in 2.46.42. Andersson is the only runner to have won the race five times, having previously come in first in four consecutive years between 2008 and 2011.

No comments:

Post a Comment