Saturday, April 13, 2013

በርካታ ቁጥር ያላቸው በስዊድን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የህውሃትን ዘረኛ ፖሊሲ አወገዙ Activists in Sweden call for greater rights


እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው በስቶክሆልምና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዓርብ ሚያዚያ ፬  (አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  እዚህ ስቶክሆልም በሚገኘው የስዊድን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፊት ለፊ ት በመገኘ ት ኢትዮጵያውያ ውስጥ በስልጣን ላይ ያለው የህውሃት መንግስትና በተለያዩ ክልሎ ች የሚገኙ ተከታዮቹ አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ላይ ያነጣጠረውንና ኢሰብዓዊ በሆነ እና ሃላፊነት በጎደለው መልኩ ከቤት ንብረታቸው የማፈናቀል ዘመቻ በማውገዝ ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቡ። የኦርቶዶክስና የእስልምና ሃይማኖት ተወካዮች በዚህ ከፍተኛ ቁጥር በነበረው የተቋውሞ ሰልፍ ላይ በመገኘት ይሄንን
በአንድ ቋንቋ ተ ናጋሪዎች ላይ የተቃጣ ዘረኛና ከፋፋይ ድርጊት ቁጣቸውን በመግለጽ በሺህ የሚቆጠሩ የእዚህ እኩይና ህገወጥ ሰለባ ወገኖቻችን በአስቸኳይ ወደ ተፈናቀሉበት ቀያቸው ተመልሰው ወደቀድሞ ህይወታቸው እንዲመለሱ አሳስበዋል። የተቋውሞ ሰልፉ አስተባባሪዎች በበኩላቸው ባሰሙት ንግግር በህውሃት መሪዎች ተቀነባብ ሮ እየተገበረ ያለውንና ዜጎች ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ በየትኛውም ክልሎች ለመኖር እና ቤት ንብረት ለማፍራት እንዳይችሉ የሚደረገውን ህገመንግስቱን የጣሰ ድርጊት እንዳስቆጣቸው በመጥቀስ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ለዚህ እኩይ ድርጊት ሳይንበረከክ ገዥው ፓርቲ ስልጣኑን ለህዝብ እንዲያሰረክብ እና ወንጀለኞቹን ለህግ በማቅረብ አስፈላጊው ቅጣት እንዲፈጸምባቸው ለጀመረው ትግሉ ከጎኑ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል። የተቋውሞ ሰልፍ አድራጊዎቹ ከዚህም
በተጨማሪ አሁን በእስር ላይ የሚገኙት እነ እስክንድር ነጋ ርዕዮት ዓለሙ ውብሸት ታዪ እና ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የህሊና እስረኞች በአስቸኳይና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ከዚህም ባሻገር መንግስት በእምነት ተቋማት ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም በህገወጥ መንገድ የታሰሩት የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጥያቂያቸውን አቅርበዋል። የእለቱን የተቋውሞ ሰልፍ የሚያንጸባርቁና ቀስቃስሽ መፈክሮችና ዘፈኖች የቀረቡ ሲሆን የተቋውሞ ሰልፉ አስተባባሪዎች ለስዊድን ተወካዮች ምክር ቤት ባስገቡት ደብዳቤ ላይ የስዊድን መንግስት ና የአውሮፓ ማህበረሰብ ይህንን ዘረ ኛና ከፋፋይ እኩይ ተግባር በማውገዝ ኢትዮጵያ ውስጥ በስልጣን ላይ ባለው መንግስት ላይ ጫና በማሳደር በህገመንግስቱ የተደነገገውን ዜጎች ያለምንም ፍራቻ የመሰብሰብ ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽና በፈለጉት የኢትዮጵያ ክልሎች የመኖር መብታቸውን እንዲያከብር ግፊት እንዲያደርጉበት ጠይቀዋል። የተቋውሞ ሰልፍ አድራጊዎቹ የህውሃት መንግስት በዜጎች ላይ እያደረገ ያለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት እስከሚያቆምና ስልጣኑን በህዝብ ለተመረጠ አካል እስከሚያስረክብ ድረስ የጀመሩትን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ለሚደረገው ትግል አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጠሉ ቃል በመግባት በስቶክሆልም መሃል ከተማ በሚገኘው የሰርጌል አደባባይ በመሰባሰብ ለሁለት ሰዓታት ያደረጉትን የተቋውሞ ሰልፍ አጠናቀዋል።

Large numbers of Ethiopians and origins of Ethiopia who reside in Stockholm and its surroundings went to the street on Friday afternoon (April 12, 2013) to express their anger over the on-going camping which targets the displacement of Amharic speaking Ethiopians from different parts of the country. The protesters condemned the eviction of Amharic language speaking innocent Ethiopians from Southern and Benishangula gumuz regions which they alleges is masterminded and geared by the ruling TPLF (Tigray People's Liberation Front) party. Religious representatives of the Ethiopian Orthodox Church and the Ethiopian Muslims on the occasion also expressed their disappointment over this unconstitutional, racist and illegal practice perpetrated against one ethnic group. They demand victims of this crime who are displaced from their lands should be returned immediately and call up on all the perpetrators to be brought to justice. Organizers of the rally on the other hand urged the government to release Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye and thousands of other Ethiopian prisoners of conscious immediately and unconditionally. They say, they went to the street to express their
outrage over TPLF's regime unconstitutional policy of evicting hardworking Ethiopians and their families from various parts of the country. The protesters also urged the government to release all leaders and followers of their Ethiopian Muslim compatriots and to stop its interference in religious matters. In a letter they submitted the Swedish Parliament, the organizers urged the Swedish government and the European Union to pressure on TPLF regime to respect its citizens' rights enshrined in the constitution. The demonstrators say they will continue their solidarity with the on-going struggle at home and abroad against the dictatorial regime until the regime transferred its power to the government elected by the people. The two hours rally is concluded down town in Stockholm.



No comments:

Post a Comment