የቅርብ አለቆቹ በጣም ሲያቸግሩት "ኢችም እንጀራ ሆና ሚጥሚጣ በዛባት" ይል ነበር አንድ ኤርሚያስ/ዩሱፍ የሚባል ጋምቤላ ከዓመታት በፊት ለመምህርነት በሄድኩበት ወቅት የተወዋወቅኩትና አሁን በህይወት የሌለ መምህር አፈሩ ይቅለልትና። በስንት ዘመኔ የረሳኋትን ተረት ለዚህ ጽሁፍ መግቢያ እንድጠቀም ያነሳሳኝ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ አንድ የጦማሬ ተከታታይ በኢትዮጵያ የጦማሬን እንዳትጎበኝ የመታገዷን ዜና እንኳን ደስ አለህ ብሎ ስላበሰረኝ ከዚህ ብስራት ጋር በተያያዘ ለመጦመር በማሰብ ነው። ለነገሩ ጦማሬ እንዲህ ዓይነት እጣ እንደሚጠብቃት ባስብም፡በትክክል እገዳው እንደተጣለባት ማረጋገጫውን እንዲሰጠኝ ጠይቄው እነሆ ዛሬ ይሄ እገዳ በትክክል እንደተደረገ ከላከልኝ ማስረጃ ለማወቅ ችያለሁ። እንዲዚህ የ የጦማሬ ተከታታይ ገለጻ ከሆነ ማንም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር የኢንተርኔት ተጠቃሚ የጦማሬን የድረ ገጽ አድራሻ www.irefugee.blogspot.com በመጻፍ ለመግባት ሲሞክር የሚከተለው የእገዳ መልእክት ይደርሰዋል።
The requested URL could not be retrieved
While trying to retrieve the URL: http://www.facebook.com/l/HAQEBMIL1AQG6vdD5h4p64gDcIwjBBV9OCBMk0sR2__mXww/irefugee.blogspot.com/2012/06/2012.html?spref=tw
The following error was encountered:
We can not connect to the server you have requested.
This means that:
The server might be busy at this time.
The server is not reachable.
Please try later to see if you can go through.
Generated Tue, 05 Jun 2012 06:46:48 GMT
While trying to retrieve the URL: http://www.facebook.com/l/HAQEBMIL1AQG6vdD5h4p64gDcIwjBBV9OCBMk0sR2__mXww/irefugee.blogspot.com/2012/06/2012.html?spref=tw
The following error was encountered:
We can not connect to the server you have requested.
This means that:
The server might be busy at this time.
The server is not reachable.
Please try later to see if you can go through.
Generated Tue, 05 Jun 2012 06:46:48 GMT
ይሄ እገዳ በትክክል ስራ ላይ የዋለው መቼ እንደሆነ በትክክል ባላውቅም ይህ ግለሰብ ጦማሬን ለመጎብኝት ባለፈው ዓርብ ሰኔ 1 2004 ዓ᎐ም᎐ ሞክሮ ሊሳካለት ባለመቻሉ ጦማሬን ለመጎብኘት ሌላ ህብኡ (ፕሮክሲ ሰርቭር) ለመጠቀም እንደተገደደ ገልጾልኛል። እኔም እገዳው በትክክል መፈጸሙን ለማረጋገጥ ባደረግኩት ማጣራት የሚከተለውን ውጤት አግኝቻለሁ። በጦማሬ ላይ በኢትዮጵያ የደህንነትና መረጃ መ/ቤት ከመጣሉ በፊት ባሉት ቀናት/ሳምንታት እና ወር ጦማሬን ከኢትዮጵያ የጎበኙት ሰዎች ቁጥር ዝርዝር ይሄን ይመስላል። ባለፈው ሳምንት





