Showing posts with label Woldeselassie Woldmicael. Show all posts
Showing posts with label Woldeselassie Woldmicael. Show all posts

Sunday, December 8, 2013

የቀድሞ የደህንነት ሀላፊ አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ልማታዊ ሙስኛ ሚሊኒየር


ኢትዮጵያ ብዙ ሚሊዮኖች ድሆች ጥቂት የተመረጠው ዘር ሚሊኒየሮች
  
ባለፈውሳምንት ኢትዮጵያ  ከአፍሪካ አገራት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ባለ ብዙ ሚሊዮን ብራሞች በማስቆጠር ዳሚነቱን እንደያዘች የተለያዩ የዜና አውታሮች  ሲግቡ ሰንብተዋል፡ 108 ከመቶ እድገት በአንድ ዓመት ብቻ በማስመዝገብ። አጃኢብ አይደል ኢትዮጵያ ቀን ወጣላት። አለፈልን ስማችን በድህነት ከመነሳት አልፎ ለዚህ ላበቃን ህውሃት እና የተከበሩ ልማታዊ ሙሰኛ አባላቱ ምስጋና ይግባቸው   እንደ አውሮፓውያኑ ቀመር 2007 ዓም ኢትዮጵያ 1300 ባለብዙ ሚሊዮን ብሮች የነበሯት ሲሆን በዚህ ዓመት ግን ቁጥራቸው ወደ ወደ 2700 አሻቅቧል የቀድሞው የደህንነት ሃላፊ አቶ ወልደሚካኤል፡ቤተሰቦቻቸው ዘመዶቻቸው፡ዘርማንዘራቸው፡ ጓደኞቻቸው፡ እነ /ሮ አዜብ መስፍን ስዩምመስፍንን፡ አቦይ ስብሃትን፡ እንዲሁም ሌሎች በአንድ ሌሊት አዳር የተተኮሱ የህውሃት አባላትን፡ደጋፊዎቻቸውንና ወዳጆቻቸውን ጨምሮ። ምን ይሳነዋል ለህውሃት። ዛሬ ፋና ሬዲዮ የዘገበው ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዴት በ1000 ብር ደሞዝ ባለ4 ደረጃ ህንጻ ማሰራት እንደሚቻል በ 500 ብር የወር ደሞዝ   በተለያዩ ባንኮች እሰከ ሚሊዮን ብር ማስቀመጥ እንደሚቻል እና ከስምንተኛ ክፍል ያቋረጡ ስራ ዓጥ እና ምንም ገቢ የሌላቸው የህውሃት ዓባላት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች እስከ 8 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር በባንክ በማስቀመጥ በአገራችን ለዘመናት ተለጥፎ የነበረውን የድህነት ምሳሌ ተረት ተረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ምን ይሳነዋል ለህውሃት? ሚሊዮኖች ጠኔ ይዟቸው በሚንጠራወዙባት ኢትዮጵያ በመቶዎች የሚቆጠሩ እንደእነ  አቶ ወልደስላሴ እና አጋሮቾቻቸው አልጠግብ ብለው ሲተፉ ያድራሉ። እስኪ ፋና ወደ አሰናዳው ዝርዝር ዜና ልመልሳችሁ።