ይህንን ጽሁፍ በእንግሊዘኛ የራሴ በሆነች ብሎግ ላይ የጻፍኩት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ቢሆንም ወደአማርኛ እንድተረጉመው ያነሳሳኝ በቅርቡ በፍትህ ጋዜጣ ላይ ""ኢትዮጵያዊ ዋጋው ስንት ነው?"" የሚለውን መጣጥፍ ካነበብኩ በኋላ ነው:: እኔ በበኩሌ የእኛ ኢትዮጵያውያን ዋጋ ተንኮታክቶ ወርዶ በዚህ ዘመን ከሌላው የሰው ዘር አይደለም ከምንም አይነት ግዑዝ ነገር በታች እንደሆነ ይሰማኛል:: ኢትዮጵያዊ መሆን አይደለም ለምን እዛች አገር ተፈጠርኩ የሚያሰኝበት ጊዜ ላይ በእርግጠኝነት ደርሰናል:: ዛሬም በገልፍ እና በሜዲትራንያንን ባህሮች ወገኖቻችን የሻርክ ሲሳይ እየሆኑ ነው: ዛሬም ወገኖቻችን በሲናይ በረሀ በበድዊን ጎሳ አባላት ለባርነት ለእስራት ለድብደባ ለአስገድዶ መድፈር እንዲሁም በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ሳያልፍ እንደ እንሰሳ እየታረዱ የውስጥና የውጭ አካል ክፍሎቻቸው እየተወሰደ ሬሳቸው በየቦታው በመጣል ላይ ይገኛል: ዛሬም እኛም ሆን መሪዎቻችን ይሄ በሰው ልጅ ታሪክ ተሰርቶ የማያውቅ ግፍ በወገኖቻችን ላይ ሲፈጸም ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ በመሆን ጭንቅላታችንን አሸዋ ውስጥ ቀብረናል:: ከዚህ በላይ ሞት ውርደት ከየት ሊመጣ:: ለዚህ እንደማስረጃነት ደግሞ ሩቅ መሄድ አያሻም: ቦሌ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በየቀኑ
መካከለኛው ምስራቅ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ኑሮ ለማሻሻል የሄዱ ሴት እህቶቻችንና ልጆቻችን ሰውነታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተቆራርጦ/ተበለሻሽቶ እድለኛ የሆኑት ደግሞ ከነሙሉ አካላቸው ሬሳቸውን መቀበል እንደተራ ነገር እየተቆጠረ ከመጣ ቆየት ብሏል:: በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች እህቶቻችን/ልጆቻችን ዛሬም በእነዚህ የአረብ አገራት በአስሪዎቻቸው ይደበደባሉ:ይንገላታሉ:ተገደው ይደፈራሉ: ይራባሉ:ይጠማሉ:በባርነት ይማቅቃሉ:ባስ ሲልም ይገደላሉ ወይም ራሳቸውን አጠፉ ተብሎ ወደ አገርቤት አስክሬናቸው አይሆኑ ሆኖ ይላካል:: ሌሎች በሺህ የሚቆጠሩ እድለኞቹ እድለኛ ከተባሉ በለበሱት ጨርቅ በእነዚህ አገራት በሚገኙ እስርቤቶች ያለማንም ጠያቂ እና ክስ ሳይመሰረትባቸው ለዐመታት ፍዳቸውን በመግፋት ላይ ይገኛሉ:: በጥቅምት ወር አጋማሽ ላይ እንኳን ሁለት እህቶቻችን በሁለት ተከታታይ ቀናት በኩዌት እና ሊባኖስ ህይወታቸውን አጥተዋል አንደኛዋ በአሰሪዋ በደረሰባት ድብደባ ሲሆን ሌላኛዋ ደግሞ
ራስዋን አጠፋች ተብሎ ምክንያት ተስጥቷል:
መካከለኛው ምስራቅ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ኑሮ ለማሻሻል የሄዱ ሴት እህቶቻችንና ልጆቻችን ሰውነታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተቆራርጦ/ተበለሻሽቶ እድለኛ የሆኑት ደግሞ ከነሙሉ አካላቸው ሬሳቸውን መቀበል እንደተራ ነገር እየተቆጠረ ከመጣ ቆየት ብሏል:: በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች እህቶቻችን/ልጆቻችን ዛሬም በእነዚህ የአረብ አገራት በአስሪዎቻቸው ይደበደባሉ:ይንገላታሉ:ተገደው ይደፈራሉ: ይራባሉ:ይጠማሉ:በባርነት ይማቅቃሉ:ባስ ሲልም ይገደላሉ ወይም ራሳቸውን አጠፉ ተብሎ ወደ አገርቤት አስክሬናቸው አይሆኑ ሆኖ ይላካል:: ሌሎች በሺህ የሚቆጠሩ እድለኞቹ እድለኛ ከተባሉ በለበሱት ጨርቅ በእነዚህ አገራት በሚገኙ እስርቤቶች ያለማንም ጠያቂ እና ክስ ሳይመሰረትባቸው ለዐመታት ፍዳቸውን በመግፋት ላይ ይገኛሉ:: በጥቅምት ወር አጋማሽ ላይ እንኳን ሁለት እህቶቻችን በሁለት ተከታታይ ቀናት በኩዌት እና ሊባኖስ ህይወታቸውን አጥተዋል አንደኛዋ በአሰሪዋ በደረሰባት ድብደባ ሲሆን ሌላኛዋ ደግሞ
ራስዋን አጠፋች ተብሎ ምክንያት ተስጥቷል:
No comments:
Post a Comment