1ኛ ሳምንታዊው አዲስ ጉዳይ መጽሄት፡ እና ሮዝ የግል አሳታሚ ድርጅት
2ኛ ሳምንታዊው ሎሚ መጽሄት፡ እና ዳዲሞስ የግል አሳታሚ ድርጅት
3ኛ በሳምንት ሁለት ጊዜ የሚታተመው እንቁ እና አለማየሁ የግል አሳታሚ ድርጅት
4ኛ ሳምንታዊ ፋክት መጽሄት እና ዮፋ የግል አሳታሚ ድርጅት
5ኛ በሳምንት ሁለት ጊዜ የሚታተመው ጃኖ መጽሄት እና አስናቀ የግል አሳታሚ ድርጅት ሲሆኑ
ስደስተኛው እና በቅርብ ጊዜ መታተም የጀመረው አፍሮ ታይምስ የተባለው ሳምንታዊ ጋዜጣ የሎሚ መጽሄት አጋር እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፡ጠቅላይ ምኒስትራችን አሜሪካን አገር በተካሄደው የአፍሮ አሜሪካ መሪዎች ስብሰባ ላይ መንግስታቸው ከምንግዜውም በበለጠ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ቁርጠኝነቱን ለፕሬዚዳንት ኦባማ እና ለተሰብሳቢዎች ገልጸዋል። ሽብርተኞቹ የተባሉት እንግዲህ፡ በማእከላዊ፡በቃሊቲ፡በቂሊንጦ፡በዝዋይ እና በሌሎች እስርቤቶች ባልሰሩት ወንጀሎች ተይዘው ክስ ሳይመሰርትባቸው ወይም በሃሰት ተወንጅለው የሚሰቃዩት የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች፡ጋዜጠኞች፡የሲቪል ተቋማት መሪዎች፡የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች እና ተከታዮቻቸው፡ እና ሌሎች በሺህ የሚቆጠሩ መሳሪያ ያልጨበጡ ኢትዮጵያውያን የጸረሽብረተኛ ህጉ ሰለባዎች ናቸው።
No comments:
Post a Comment